በተደጋጋሚ የሚጠየቁ

Frequently Asked Questions

2. ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ብቁ የሆነው ማነው?

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ህጋዊ ነዋሪ በሙሉ ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ብቁ ነው። በ “ረቂቅ አዋጁ” ነዋሪ የሚገለፀው  “በህጋዊ መልኩ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ፣ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያለው ወይም የሌለው የተፈጥሮ ሰው እንዲሁም በሀገሪቱ ህግ መሰረት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ወይም የሚሰራ የውጭ ሀገር ዜጋ ነው።” ይህም የሚያካትተው ፡- 

  • ዕድሜያቸው ከ 5 ዓመት በላይ የሆኑ ልጆች መመዝገብ ይችላሉ.
    ከ 5 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት, በቅርቡ ልዩ የምዝገባ ፕሮግራም የምንጀምር ይሆናል።
  • ኢትዮጵያዊ እና ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ የነዋሪነት ማረጋገጫ ያላቸው
  • የመኖሪያ አድራሻ ማረጋገጫ ሰነድ ያላቸውም ሆነ የሌላቸው ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪነታቸው “በአዋጁ መሰረት” የተሰጠ። 
  • የት እንደሚኖሩ ምንም ዓይነት ሰነድ የሌላቸው ሰዎች ፣ የዲጂታል መታወቂያ ያለው ሰው እንደ ምስክር ይዞ በመቅረብ መመዝገብ ይችላሉ።
  • ማንኛውም ለምዝገባ ብቁ የሆነ ሰው id.et/proof ላይ በተጠቀሰው መሰረት  ተቀባይነት ያለው የማንነት ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርበታል።

አማርኛ